top of page
ዘረኝነት በዚህ ያብቃ !

የፕሮጀክት፦ክትትል ዘረኝነትን ለመዋጋት የፓልመርሪፖርት ምክሮችና ሃሳቦች ፤ 

CC BY-SA 4.0: dujerit

ኮሚቴው  መከረ፤ መንግስት አጸደቀ በተግባርስ ምን እየተደረገ ነው ?​

በ2015 ዓ.ም ወጣት ኢትዮጵያውያን በደልና ዘረኝነት በዛብን ብለው የተለያዩ ሰላማዊ ሰልፎችን 
በማዘጋጀት ድምጻቸውን አሰሙ ። ለዚህ መነሻ የሆናቸውም ለረዥም  ጊዜ እየተፈጸመ የቀጠለውን በደልና መሳናክሎች ስለመረራቸው ነበር ፡፡  በተለያዩ ቦታዎች  በስራ ቦታዎች፤  በትምህርት ተቋማት ፤ ህግ በተዛባ መልኩ በተሰጡ ፍርዶች ቁጥራቸው ከህብረተሰቡ ቁጥር አንጻር ብዙ የሆኑ ወጣቶች ለእስር ተዳርገዋል  ፡፡ 
በዚህ ምክንያት ዘረኝነትን ለመዋጋት የተለያዩ መ/ቤቶች ባለሙያዎችን ያካተተ ተቋም እንዲመሰረት ተወሰነ ፡፡
በሐምሌ 2016 ዓ.ም በፍትህ ሚኒስትር ስራ አስኪያጅ ስም የተሰየመው የፓልመር ኮሚቴ ሪፖርቱን አቀረበ  የተወሰኑ ሃሳቦችም በመንግስት ውሳኔዎች ተስተካክለው ነበር ።
ከቀረበው ሪፖርት አንደኛው ውሳኔም  በመንግስት ቁጥጥር ስር የሆነ ዘረኝነትና አድልዎን የሚዋጋና ቢሮክራሲን የሚያስወግድ ሁሉም በእኩልነት መንገድ የሚያስተናግዱበት መንገዶች እንዲያመቻች በማቀድ ነው ።
ምንም እንኳን  ይህ ሪፖርት መነሻውና ትኩረት ያደረገው በኢትዮጵያ ይሁዳውያን  ችግር ላይ ቢሆንም ሌሎች የእስራኤል ህብረተሰብ ክፍሎች ማለትም  እንደ አረቦች ፤ከአረብ ሀገራት የመጡ ይሁዲዎች  ፤ሌዚቢያን ፤ጌዎች አካለ ስንኩላን ፤ ማየት የተሳናቸውን በስደት ወደ እስራኤል የገቡ የሌላ ሀገር ዜጎች ላይ የሚከሰቱ ጉዳዮችንም ያካትታል ። በተለያዩ ቦታዎች ማለትም በየመስሪያ ቤቱ በየትምህርት  ተቋማት ፤ የሚከሰቱ መሰናክሎች ኋላ ቀር አመለካከቶች፤ ጥላቻወችን ከወዲሁ ለመቅረፍ እንዲረዳ የታቀደ ነው ፡ ስለዚህ  የፓልመር ኮሚቴ የሰጠው  ሃሳብ በእነርሱም  ተፈጻሚነት ይኖረዋል ማለት ነው ።
 የዜጎች መብት አስከባሪና ተቆርቋሪ ድርጅት ከዜጎች እውቀት ማጎልመሻ ድርጅትና የዜጎችን አቅም ማዳበሪያ ማሰልጠኛ ማእከል ተቋማት ጋር በመተባበር የፓልመር ሪፖርት ያቀረበውን 16 ሃሳቦች ይፈትሻል ይከታተላል ። በስራ ላይ መዋላቸውን ይከታተላል ።
እኛም እነዚህ የመረጥናቸው  16 ሃሳቦች  በህብረተሰባችን ውስጥ ዘረኝነትና አድልዎ እንዳይስፋፋና እንዳይቀጥል ምክንያት ሆነው ስላገኘናቸው ነው ።
እነዚህ ሃሳብና አስተያየቶች ስራ ላይ ከዋሉ በሀገራችን ተንሰራርቶ የሚገኘው ዘረኝነትና አድልዎን  ለመቅረፍ በጣም ይረዳሉ ብለን እንገምታለን ።
እኛም በዚህ ድህረ ገጽ የቀረቡትን ሃሳቦች ፤ የተወሰኑ ውሳኔዎች ተግባራዊ መሆናቸውን ዘረኝነትንና አድሎን ለማስወገድ የተደረጉ እንቅስቃሴዎችን እናቀርባለን  ። ድህረ ገጹምቀጣይነት ባለው መንገድ ወቅታዊ ዜናዎችን ያቀርባል ፦ የቀረበውን የምክር ሃሳብ ለመመልከት ምስሉን ይጫኑ ! 

Amharic-recs

የዜጎች መብት ተቆርቋሪና አስከባሪ ድርጅት ዘረኝነትና አድሎን ለመታገል ያደረጉትን የስራ እንቅስቃሴ በተመለከተ እዚህ ላይ ይጫኑ ! ( እብራይስጥ )

ዘረኝነትን በተመለከተ ለሚቀርቡ ትምህርታዊ መረጃዎች እዚህ ላይ ይጫኑ ! (እብራይስጥ )

አድሎና በደል ደርሶብዎታል ? የዜጎች መብት ተቆርቋሪና አስከባሪ ድርጅት ሰራተኞች ጋር አቤቱታ ያሰሙ !

Photos: Dreamstime.com, © Rafael Ben Ari | Dreamstime.com, Keren Manor, Activestills, © Fotokon | Dreamstime.com

Funded by the European Union.

The content of this minisite
is the exclusive responsibility of the ACRI
and should in no way be considered
to reflect the view of the European Union.

האגודה לזכויות האזרח בישראל

נחלת בנימין 75 תל אביב

  03-5608185

 www.acri.org.il | mail@acri.org.il

  • האגודה באינסטגרם
  • האגודה בטוויטר
  • האגודה בפייסבוק

התכנים באתר (חוץ מהתמונות) מופצים תחת רישיון CC BY-NC-SA.

bottom of page